ኔታንያሁ የኒው ዮርክ ከንቲባን “ጥላቻን በማነሳሳት” ወነጀሉ
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የኒው ዮርክ ከንቲባ በቁጥጥር ስር ሊያውሏቸው ቢዝቱም በመንግሥታቱ ድርጅት ጉባዔ ላይ ለመታደም ማቀዳቸውን ተናገሩ።
የኒው ዮርክ ከንቲባ የሆኑት ዞህራን ማምዳኒ ባለፈው ሳምንት ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ያወጣውን የእስር ማዘዣ ለማስፈጸም ተናግረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ የሕግ ድጋፍ እንደሌላቸው በመግለጽ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ለፎክስ ኒውስ እሁድ ዕለት እንደተናገሩት ማምዳኒ ቀደም ሲሉ በሰጡት አስተያየት “ስጋት እንደማይገባቸው”ተናግረው ከንቲባው “ጥላቻን ያነሳሳሉ” ሲሉ ወንጅለዋቸዋል።
ኔታንያሁ “እርሱ የሁሉም የኒውዮርክ ነዋሪዎች፣ አይሁዶች፣ ክርስቲያኖች፣ ሙስሊሞች ከንቲባ መሆን አለበት፤ ነገር ግን አንዱን ቡድን በሌላኛው ላይ ለማነሳሳት እየሞከረ ነው” ሲሉተናግረዋል።
ኔታንያሁ ሐሙስ ዕለት በኒው ዮርክ የተፈፀመውን ሁለት የስለት ጥቃት ጠቅሰዋል፤ በዚህ ጥቃት አንድ ተጠርጣሪ አንድ አይሁዳዊ እና አንድ እስያዊን ወግቷል።
ፖሊሶች ተጠርጣሪው በስለት ጥቃት ሲያደርስ "አላህ አክበር" እያለ ይጮህ ነበር። ከእያንዳንዱ ተጎጂ ጋር በተያያዘ በጥላቻ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶበታል።
ሁለቱም ሰዎች ከጥቃቶቹ የተረፉ ሲሆን ይህም ከከተማዋ የአይሁድ እና የእስያ አሜሪካውያን መሪዎች ውግዘት አስከትሏል።
ከዚያ በኋላ ኔታንያሁ በሰጡት ቃለ ምልልስ በኒው ዮርክ የሚኖሩ አይሁዶች "ፈርተዋል" ብለዋል።